ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 53:5-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. ነገር ግን እርሱ ስለ መተላለፋችን ተወጋ፤ስለ በደላችንም ደቀቀ፤በእርሱ ላይ የወደቀው ቅጣት ለእኛ ሰላም አመጣልን፤በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።

6. እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤እያንዳንዳችንም በየመንገዳችን ነጐድን፤ እግዚአብሔርም፣ የሁላችንን በደልበእርሱ ላይ ጫነው።

7. ተጨነቀ፤ ተሠቃየም፤ነገር ግን አፉን አልከፈተም፤እንደ ጠቦትም ለዕርድ ተነዳ፤በሸላቾች ፊት ዝም እንደሚል በግ፣አፉን አልከፈተም።

8. በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ስለ ሕዝቤ ኀጢአት ተመቶ፣ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ፣ከትውልዱ ማን አስተዋለ?

9. በአፉ ተንኰል ሳይገኝበት፣ምንም ወንጀል ሳይሠራ፣አሟሟቱ ከክፉዎች፣መቃብሩም ከባለጠጎች ጋር ሆነ።

10. መድቀቁና መሠቃየቱ ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር፤ እግዚአብሔር ነፍሱን የኀጢአት መሥዋዕት ቢያደርገውም እንኳ፣ዘሩን ያያል፤ ዕድሜውም ይረዝማል፤ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።

11. ከነፍሱ ሥቃይ በኋላ፣የሕይወት ብርሃን ያያል፤ ደስም ይለዋል፤ጻድቅ ባሪያዬ በዕውቀቱ ብዙዎቹን ያጸድቃል፤መተላለፋቸውንም ይሸከማል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 53