ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 5:7-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርየወይን ቦታው የእስራኤል ቤት ነው፤የይሁዳ ሰዎችምየደስታው አትክልት ናቸው።ፍትሕን ፈለገ፤ ነገር ግን ደም ማፍሰስን አየ፤ጽድቅን ፈለገ፤ ነገር ግን የጭንቅን ጩኸት ሰማ።

8. ስፍራ ለሌሎች እስከማይተርፍ፣ቤትን በቤት ላይ በመጨመር፣መሬትን ከመሬት ጋር በማያያዝ፣ለብቻችሁ በምድር ተስፋፍታችሁ ለምትኖሩ ወዮላችሁ

9. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ጆሮዬ እየሰማ እንዲህ ሲል ተናገረ፤“ታላላቅ ቤቶች ወና ይቀራሉ፣የሚያማምሩም ቤቶች ኗሪ ያጣሉ።

10. ከሩብ ጋሻ የወይን ቦታ አንድ የባዶስ መስፈሪያ ያህል የወይን ጭማቂ ብቻ ይገኛል፤ አንድ የቆሮስ መስፈሪያ ዘር ተዘርቶ አንድ የኢፍ መስፈሪያ እህል ብቻ ይሰጣል።

11. የሚያሰክር መጠጥ ፍለጋማልደው ለሚነሡ፣እስኪያነዳቸውም ወይን በመጠጣትሌሊቱን ለሚያነጉ ወዮላቸ

12. በግብዣቸው ላይ በገናና መሰንቆ፣ከበሮና ዋሽንት እንዲሁም የወይን ጠጅ አለ፤ነገር ግን ለእግዚአብሔር ሥራ ቦታ አልሰጡም፤ለእጆቹም ሥራ ክብር አላሳዩም።

13. ስለዚህ ሕዝቤዕውቀት በማጣቱ ይማረካል፤መኳንንቱም በራብ ይሞታሉ፤ሕዝቡም በውሃ ጥም ይቃጠላል።

14. ስለዚህ ሲኦል ሆዷን አሰፋች፣አፏንም ያለ ልክ ከፈተች፤መኳንንቱና ሕዝቡ ከረብሸኞቻቸውና ከጨፋሪዎቻቸው ጋርወደዚያ ይወርዳሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 5