ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 42:9-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. እነሆ፤ የቀድሞው ነገር ተፈጽሞአል፤እኔም አዲስ ነገር እናገራለሁ፤ከመብቀሉም በፊት፣ለእናንተ አስታውቃለሁ።

10. እናንት ወደ ባሕር የምትወርዱ፣ በዚያም ያላችሁ ሁሉ፣ደሴቶችና በዚያ የምትኖሩ በሙሉ፣ ለእግዚአብሔር አዲስ መዝሙር፣ከምድር ዳርቻም ምስጋናውን ዘምሩ።

11. ምድረ በዳውና ከተሞቹ ድምፃቸውን ከፍ ያድርጉ፤ቄዳር ያለችበት መንደር ደስ ይበለው፤የሴላ ሕዝቦች በደስታ ይዘምሩ፤ከተራሮችም ራስ ላይ ይጩኹ።

12. ክብር ለእግዚአብሔር ይስጡ፤ምስጋናውንም በደሴቶች ያውጁ።

13. እግዚአብሔር እንደ ኀያል ሰው ይዘምታል፤እንደ ተዋጊ በወኔ ይነሣል፤የቀረርቶ ጩኸት ያሰማል፤ጠላቶቹንም ድል ያደርጋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 42