ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 41:15-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

15. “እነሆ፣ አዲስየተሳለና ብዙ ጥርስ ያለው ማሄጃ አደርግሃለሁ፤ተራሮችን ታሄዳለህ፤ ታደቃቸዋለህ፤ኰረብቶችንም ገለባ ታደርጋቸዋለህ።

16. ታበጥራቸዋለህ፤ ነፋስ ጠርጎ ይወስዳቸዋል፤ዐውሎ ነፋስም ይበትናቸዋል።አንተ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይልሃል፤በእስራኤል ቅዱስ ሞገስ ታገኛለህ።

17. “ድኾችና ችግረኞች ውሃ ይፈልጋሉ፤ዳሩ ግን ምንም አያገኙም፤ጒሮሮአቸው በውሃ ጥም ደርቆአል።ነገር ግን እኔ እግዚአብሔር እመልስላቸዋለሁ፤እኔ የእስራኤል አምላክ አልተዋቸውም።

18. በተራቈቱ ኰረብቶች ላይ ወንዞችን፣በሸለቆዎች ውስጥ ምንጮች አፈልቃለሁ።ምድረ በዳውን የውሃ ኵሬ፣የተጠማውን ምድር የውሃ ምንጭ አደርጋለሁ።

19. በምድረ በዳ፣ዝግባን፣ ግራርን፣ ባርሰነትንና ወይራን አበቅላለሁ፤በበረሃ፣ ጥድን፣ አስታንናሸውሸዌን በአንድነት እተክላለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 41