ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 22:12-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. በዚያን ቀን ጌታ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣እንድታለቅሱና በዋይታ እንድትጮኹ፣ጠጒራችሁን እንድትነጩማቅም እንድትለብሱ ጠራችሁ።

13. ነገር ግን እነሆ፤ ተድላና ደስታ፣ፍሪዳ መጣልና ሙክት ማረድ፣ሥጋ መብላትና የወይን ጠጅ መጠጣት አለ፤“እንብላ እንጠጣነገ እንሞታለንና” አላችሁ።

14. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ይህን ገለጠልኝ፤ እንዲህም ሲል በጆሮዬ ሰማሁ፤ “ይህ ኀጢአት እስከምትሞቱበት ቀን ድረስ አይሰረይላችሁም” ይላል ጌታ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር።

15. ጌታ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ሂድና ይህን መጋቢ፣የቤቱንም ኀላፊ ሳምናስን እንዲህ በለው፤

16. ‘እዚህ ምን ታደርጋለህ?በዚህ ስፍራ ለራስህ መቃብርን እንድ ታዘጋጅ፣በከፍታውም ላይ መቀበሪያህን እንድ ትወቅር፣ሬሳህ የሚያርፍበትንም ዐለት እንድ ትጠርብ ማን ፈቀደልህ?’

17. አንተ ኀያል ሰው ሆይ፤ ተጠንቀቅ፤ እግዚአብሔር አጥብቆ ሊይዝህ፣ በእጆቹም ጨብጦ ሊወረውርህ ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 22