ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሚክያስ 4:7-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. የሽባዎችን ትሩፍ፣የተገፉትንም ብርቱ ሕዝብ አደርጋለሁ፤ከዚያች ቀን አንሥቶ እስከ ዘላለም፣ እግዚአብሔር በጽዮን ተራራ በእነርሱ ላይ ይነግሣል።

8. አንተ የመንጋው መጠበቂያ ማማ ሆይ፤የጽዮን ሴት ልጅ ዐምባ ሆይ፤የቀድሞው ግዛትህ ይመለስልሃል፤የመንግሥትም ሥልጣን ለኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ይሆናል።”

9. አሁንስ እንደዚህ የምትጮኺው ለምንድን ነው?ንጉሥ የለሽምን?ምጥ እንደ ያዛት ሴት የተጨነቅሽው፣መካሪሽ ስለ ጠፋ ነውን?

10. የጽዮን ሴት ልጅ ሆይ፤ምጥ እንደ ያዛት ሴት ተጨነቂ፤አሁንስ ከከተማ ወጥተሽ፣በሜዳ ላይ መስፈር አለብሽና፤ወደ ባቢሎን ትሄጃለሽ፣በዚያ ከጠላት እጅ ትድኛለሽ፤ እግዚአብሔር በዚያ፣ከጠላቶችሽ ይታደግሻል።

11. አሁን ግን ብዙ አሕዛብ፣በአንቺ ላይ ተሰብስበዋል፤እነርሱም፣ “የረከሰች ትሁን፤ዐይናችንም ጽዮንን መዘባበቻ አድርጎ ይያት” ይላሉ።

12. ነገር ግን የእግዚአብሔርን ሐሳብ አያውቁም፤በአውድማ ላይ እንደ ነዶየሚሰበስባቸውን፣የእርሱን ዕቅድ አያስተውሉም።

13. የጽዮን ልጅ ሆይ፤ ተነሥተሽ አበራዪ፤የብረት ቀንድ እሰጥሻለሁና፤የናስ ሰኰና እሰጥሻለሁ፤አሕዛብንም ታደቂያቸዋለሽ።”በግፍ ያግበሰበሱትን ትርፍ ለእግዚአብሔር፣ሀብታቸውንም ለምድር ሁሉ ጌታ ታቀርቢያለሽ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሚክያስ 4