ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መክብብ 5:1-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ወደ እግዚአብሔር ቤት ስትሄድ እግርህን ጠብቅ። ለመስማት መቅረብ የሰነፎችን መሥዋዕት ከማቅረብ ይበልጣል፤ እነርሱ ክፉ እንደሚሠሩ አያውቁምና።

2. በአፍህ አትፍጠን፤በእግዚአብሔርም ፊት ማንኛውንም ነገር ለመናገር፣በልብህ አትቸኵል፤እግዚአብሔር በሰማይ፣አንተ ደግሞ በምድር ነህ፤ስለዚህ ቃልህ ጥቂት ይሁን።

3. በሥራ ብዛት ሕልም እንደሚታይ፣ብዙ ቃል ባለበትም የሞኝ ንግግር ይገለጣል።

4. ለእግዚአብሔር ስእለትን በተሳልህ ጊዜ ለመፈጸም አትዘግይ፤ በሰነፎች ደስ አይለውምና፤ ስእለትህን ፈጽም።

5. ስእለት ተስሎ ካለመፈጸም፣ አለመሳል ይሻላል።

6. አንደበትህ ወደ ኀጢአት እንዲመራህ አትፍቀድ፤ ለቤተ መቅደስ መልእክተኛም፣ “የተሳልሁት በስሕተት ነበር” አትበል። እግዚአብሔር በተናገርኸው ተቈጥቶ የእጅህን ሥራ ለምን ያጥፋ?

7. ብዙ ሕልምና ብዙ ቃል ከንቱ ነው፤ ስለዚህ እግዚአብሔርን ፍራ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መክብብ 5