ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሕዝቅኤል 30:16-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. በግብፅ ላይ እሳት አነዳለሁ፤ሲን በጭንቅ ትናጣለች፤ቴብስ በማዕበል ትወሰዳለች፤ሜምፊስ በማያቋርጥ ጭንቀት ውስጥ ትገባለች።

17. የሄልዮቱና የቡባስቱ ጐልማሶች፣በሰይፍ ይወድቃሉ፤ከተሞቹ ራሳቸውም ይማረካሉ።

18. የግብፅን ቀንበር በምሰብርበት ጊዜ፣በጣፍናስ ቀኑ ይጨልማል፤ከዚያም የተኵራራችበት ብርታት ይንኰታኰታል።በደመና ትሸፈናለች፤መንደሮቿም ይማረካሉ።

19. ስለዚህ በግብፅ ላይ ቅጣቴን አመጣለሁ፤እነርሱም እኔ እግዚአብሔር እንደሆንሁ ያውቃሉ።’ ”

20. በዐሥራ አንደኛው ዓመት፣ በመጀመሪያው ወር በሰባተኛው ቀን፣ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤

21. “የሰው ልጅ ሆይ፤ የግብፅን ንጉሥ የፈርዖንን ክንድ ሰብሬአለሁ፤ ይፈወስ ዘንድ ክንዱ አልተጠገነም፤ ወይም ሰይፍ መያዝ ይችል ዘንድ እጁ በመቃ አልታሰረም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሕዝቅኤል 30