ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሮሜ 9:27-33 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

27. ኢሳይያስም ስለ እስራኤል እንዲህ ሲል ይጮኻል፤“የእስራኤል ልጆች ቊጥር በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ ቢሆንም፣ትሩፉ ብቻ ይድናል።

28. ጌታ ፍርዱን በምድር ላይ፣በፍጥነትና ለመጨረሻ ጊዜ ይፈጽማልና።”

29. ይኸውም ቀደም ሲል ኢሳይያስእንደ ተናገረው ነው፤“የሰራዊት ጌታ፣ ዘር ባያስቀርልን ኖሮ፣እንደ ሰዶም በሆን ነበር፤ገሞራንም በመሰልን ነበር።”

30. እንግዲህ ምን እንበል? በእምነት የሆነውን ጽድቅ፣ ለጽድቅ ያልደከሙት አሕዛብ አገኙት፤

31. ነገር ግን የጽድቅን ሕግ የተከታተሉት እስራኤል አላገኙትም።

32. ይህ ለምን ሆነ? በእምነት ሳይሆን በሥራ እንደሆነ አድርገው በመቊጠር ስለ ተከታተሉት ነው፤ እነርሱም፣ “በማሰናከያው ድንጋይ” ተሰናከሉ።

33. ይህም፣“እነሆ፤ ሰዎችን እንዲደናቀፉ የሚያደርግ ድንጋይ፣እንዲወድቁ የሚያደርግ ዐለት፣በጽዮን ላይ አስቀምጣለሁ፤ በእርሱም የሚያምን አያፍርም”ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሮሜ 9