ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሮሜ 9:23-29 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

23. አስቀድሞ ለክብር ላዘጋጃቸው፣ የምሕረቱም መግለጫዎች ለሆኑት፣ የክብሩ ባለጠግነት እንዲታወቅ ይህን አድርጎ እንደሆነስ?

24. የጠራው ከአይሁድ ወገን ብቻ ሳይሆን ከአሕዛብ ወገን የሆነውን እኛን እንኳ ሳይቀር አይደለምን?

25. በሆሴዕ እንዲህ እንደሚል፤“ሕዝቤ ያልሆኑትን፣ ‘ሕዝቤ’ ብዬ እጠራቸዋለሁ”፤ያልተወደደችውንም ‘የተወደደችው’ ብዬ እጠራለሁ።

26. ደግሞም፣ “ ‘ሕዝቤ አይደላችሁም’፤ተብሎ በተነገራቸው በዚያ ቦታ፣‘የሕያው እግዚአብሔር ልጆች’ ተብለውይጠራሉ።”

27. ኢሳይያስም ስለ እስራኤል እንዲህ ሲል ይጮኻል፤“የእስራኤል ልጆች ቊጥር በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ ቢሆንም፣ትሩፉ ብቻ ይድናል።

28. ጌታ ፍርዱን በምድር ላይ፣በፍጥነትና ለመጨረሻ ጊዜ ይፈጽማልና።”

29. ይኸውም ቀደም ሲል ኢሳይያስእንደ ተናገረው ነው፤“የሰራዊት ጌታ፣ ዘር ባያስቀርልን ኖሮ፣እንደ ሰዶም በሆን ነበር፤ገሞራንም በመሰልን ነበር።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሮሜ 9