ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሮሜ 3:9-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. እንግዲህ ምን እንላለን? እኛ ከእነርሱ እንበልጣለንን? ከቶ አይደለም፤ አይሁድም ሆኑ አሕዛብ፣ ሁሉም ከኀጢአት በታች እንደሆኑ አስቀድመን ከሰናቸዋል፤

10. እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፤“ጻድቅ ማንም የለም፤ አንድም እንኳ፤

11. አስተዋይ የለም፤እግዚአብሔርንም የሚሻ አንድም የለም።

12. ሁሉም ተሳስተዋል፤በአንድነት የማይጠቅሙ ሆነዋል፤በጎ የሚያደርግ ማንም የለም፤አንድም እንኳ።”

13. “ጒሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤አንደበታቸው ሽንገላን ያዘወትራል።”“በከንፈሮቻቸው የእባብ መርዝ አለ።”

14. “አፋቸው ርግማንና ምሬት ሞልቶበታል።”

15. “እግራቸው ደም ለማፍሰስ ፈጣን ነው፤

16. በመንገዳቸው ጥፋትና ጒስቊልና ይገኛል፤

17. የሰላምንም መንገድ አያውቁም።”

18. “በዐይናቸው ፊት የእግዚአብሔር ፍርሀት የለም።”

19. እንግዲህ አፍ ሁሉ እንዲዘጋና ዓለም በሙሉ ለእግዚአብሔር መልስ እንዲሰጥ ሕግ የሚናገረው ሁሉ ከሕግ በታች ላሉት እንደሆነ፣ እናውቃለን፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሮሜ 3