ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሮሜ 3:12-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. ሁሉም ተሳስተዋል፤በአንድነት የማይጠቅሙ ሆነዋል፤በጎ የሚያደርግ ማንም የለም፤አንድም እንኳ።”

13. “ጒሮሮአቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤አንደበታቸው ሽንገላን ያዘወትራል።”“በከንፈሮቻቸው የእባብ መርዝ አለ።”

14. “አፋቸው ርግማንና ምሬት ሞልቶበታል።”

15. “እግራቸው ደም ለማፍሰስ ፈጣን ነው፤

16. በመንገዳቸው ጥፋትና ጒስቊልና ይገኛል፤

17. የሰላምንም መንገድ አያውቁም።”

18. “በዐይናቸው ፊት የእግዚአብሔር ፍርሀት የለም።”

19. እንግዲህ አፍ ሁሉ እንዲዘጋና ዓለም በሙሉ ለእግዚአብሔር መልስ እንዲሰጥ ሕግ የሚናገረው ሁሉ ከሕግ በታች ላሉት እንደሆነ፣ እናውቃለን፤

20. ስለዚህ ሕግን በመጠበቅ ማንም በእርሱ ፊት ጻድቅ ነው ሊባል አይችልም፤ ይልቁንም በሕግ አማካይነት ኀጢአትን እንገነዘባለን።

21. አሁን ግን ሕግና ነቢያት የመሰከሩለት፣ ከሕግ ውጭ የሆነ፣ የእግዚአብሔር ጽድቅ ተገልጦአል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሮሜ 3