ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሮሜ 14:10-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. ታዲያ አንተ በወንድምህ ላይ ለምን ትፈርዳለህ? ለምንስ ወንድምህን ትንቃለህ? ሁላችንም በእግዚአብሔር የፍርድ ወንበር ፊት እንቀርባለንና፤

11. እንዲህ ተብሎ ተጽፎአል፤“ ‘እኔ ሕያው ነኝና’፤‘ጒልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል፤ምላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር ይመሰክራል’ ” ይላል ጌታ።

12. ስለዚህ እያንዳንዳችን ስለ ራሳችን ለእግዚአብሔር መልስ እንሰጣለን።

13. ስለዚህ እርስ በርሳችን፣ አንዱ በሌላው ላይ ከመፍረድ እንቈጠብ፤ በዚህ ፈንታ ግን በወንድምህ መንገድ ላይ የማሰናከያ ድንጋይ ወይም ወጥመድ እንዳታስቀምጥ ቊርጥ ሐሳብ አድርግ።

14. በጌታ በኢየሱስ ሆኜ በራሱ ንጹሕ ያልሆነ ምንም ምግብ እንደሌለ ተረድቻለሁ፤ ነገር ግን አንድ ሰው አንድን ነገር ንጹሕ እንዳልሆነ የሚቈጥር ከሆነ፣ ያ ነገር ለእርሱ ንጹሕ አይደለም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሮሜ 14