ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሮሜ 11:26-31 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

26. ስለዚህ እስራኤል ሁሉ ይድናሉ፤ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፤“አዳኝ ከጽዮን ይወጣል፤ከያዕቆብም ክፋትን ያስወግዳል።

27. ኀጢአታቸውንም ሳስወግድ፣ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳኔ ይህ ነው።”

28. እንደ ምሥራቹ ቃል ለእናንተ ሲባል ጠላቶች ናቸው፤ እንደ ምርጫ ከሆነ ግን፣ ለአባቶች ሲባል የተወደዱ ናቸው፤

29. የእግዚአብሔር ስጦታና ጥሪ ጸጸት የለበትም።

30. እናንተም ቀድሞ ለእግዚአብሔር የማትታዘዙ እንደ ነበራችሁ፣ ከእነርሱ አለመታዘዝ የተነሣ አሁን ምሕረት እንዳገኛችሁ ሁሉ፣

31. እግዚአብሔር ለእናንተ ምሕረት ከማድረጉ የተነሣ፣ እነርሱም ምሕረት ያገኙ ዘንድ አሁን የማይታዘዙ ልጆች ሆነዋል፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሮሜ 11