ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሮሜ 11:25-36 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

25. ወንድሞች ሆይ፤ ልባሞች የሆናችሁ እንዳይመስላችሁ፣ ይህን ምስጢር ሳታውቁ እንድትቀሩ አልፈልግም፤ የአሕዛብ ሙላት እስኪገባ ድረስ፣ እስራኤል በከፊል በድን ዳኔ ውስጥ ዐልፋለች።

26. ስለዚህ እስራኤል ሁሉ ይድናሉ፤ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፤“አዳኝ ከጽዮን ይወጣል፤ከያዕቆብም ክፋትን ያስወግዳል።

27. ኀጢአታቸውንም ሳስወግድ፣ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳኔ ይህ ነው።”

28. እንደ ምሥራቹ ቃል ለእናንተ ሲባል ጠላቶች ናቸው፤ እንደ ምርጫ ከሆነ ግን፣ ለአባቶች ሲባል የተወደዱ ናቸው፤

29. የእግዚአብሔር ስጦታና ጥሪ ጸጸት የለበትም።

30. እናንተም ቀድሞ ለእግዚአብሔር የማትታዘዙ እንደ ነበራችሁ፣ ከእነርሱ አለመታዘዝ የተነሣ አሁን ምሕረት እንዳገኛችሁ ሁሉ፣

31. እግዚአብሔር ለእናንተ ምሕረት ከማድረጉ የተነሣ፣ እነርሱም ምሕረት ያገኙ ዘንድ አሁን የማይታዘዙ ልጆች ሆነዋል፤

32. እግዚአብሔር ለሁሉም ምሕረት ያደርግ ዘንድ ሰውን ሁሉ ባለመታዘዝ ዘግቶታልና።

33. የእግዚአብሔር የጥበቡና የዕውቀቱ ባለጠግነት እንዴት ጥልቅ ነው!ፍርዱ አይመረመርም፤ለመንገዱም ፈለግ የለው … 

34. “የጌታን ልብ ያወቀ ማነው?አማካሪውስ የነበረ ማን ነው?”

35. “እግዚአብሔር መልሶ እንዲሰጠው፣ለእግዚአብሔር ያበደረ ከቶ ማን ነው?”

36. ሁሉም ከእርሱ፣ በእርሱ፣ ለእርሱ ነውና፤ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሮሜ 11