ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ራእይ 7:7-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ከስምዖን ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣ከሌዊ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣ከይሳኮር ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣

8. ከዛብሎን ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣ከዮሴፍ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣ከብንያም ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ ታተሙ።

9. ከዚህም በኋላ አየሁ፤ እነሆ፤ በዙፋኑና በበጉ ፊት ማንም ሊቈጥራቸው የማይችል ከሕዝብ፣ ከነገድ፣ ከወገን፣ ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሕዝብ ቆመው ነበር፤ እነርሱም ነጭ ልብስ ለብሰው፣ የዘንባባ ዝንጣፊ በእጃቸው ይዘው ነበር።

10. በታላቅ ድምፅም እንዲህ ብለው ጮኹ፤“ማዳን በዙፋኑ ላይ የተቀመጠው፣የአምላካችንና የበጉ ነው።”

11. መላእክቱም ሁሉ በዙፋኑና በሽማግሌዎቹ፣ በአራቱም ሕያዋን ፍጡራን ዙሪያ ቆመው ነበር፤ በዙፋኑ ፊት በግንባራቸው ተደፍተው ለእግዚአብሔር ሰገዱ፤

12. እንዲህም ይሉ ነበር፤“አሜን፤ውዳሴና ክብር፣ጥበብ፣ ምስጋናና፣ ሞገስ፣ኀይልና ብርታትም፣ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ለአምላካችን ይሁን፤አሜን።”

13. ከዚያም ከሽማግሌዎቹ አንዱ፣ “እነዚህ ነጭ ልብስ የለበሱት እነማን ናቸው? ከወዴትስ መጡ?” አለኝ።

14. እኔም፣ “ጌታ ሆይ፤ አንተ ታውቃለህ” አልሁት።እርሱም እንዲህ አለኝ፤ እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው፤ ልብሳቸውንም በበጉ ደም አጥበው “አንጽተዋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ራእይ 7