ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ራእይ 5:10-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. ለአምላካችንም መንግሥትና ካህናት አድርገሃቸዋል፤እነርሱም በምድር ላይ ይነግሣሉ።”

11. ከዚያም ተመለከትሁ፤ የብዙ መላእክትን ድምፅ ሰማሁ፤ ቍጥራቸውም ሺህ ጊዜ ሺህና እልፍ ጊዜ እልፍ ነበረ፤ እነርሱም በዙፋኑና በሕያዋን ፍጡራኑ፣ በሽማግሌዎቹም ዙሪያ ከበው ነበር፤

12. በታላቅ ድምፅም እንዲህ ብለው ዘመሩ፤“የታረደው በግ ኀይልና ባለጠግነት፣ጥበብና ብርታት፣ክብርና ሞገስ፣ ምስጋናም፣ሊቀበል ይገባዋል።

13. ከዚያም በሰማይና በምድር፣ ከምድር በታችና በባሕር፣ በእነርሱ ውስጥ ያሉ ፍጡራንም ሁሉ እንዲህ ብለው ሲዘምሩ ሰማሁ፤“በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠውና ለበጉ፣ምስጋናና ሞገስ፣ ክብርና ኀይል፣ከዘላለም እስከ ዘላለም ይሁን።”

14. አራቱ ሕያዋን ፍጡራንም፣ “አሜን” አሉ፤ ሽማግሌዎቹም በግምባራቸው ተደፍተው ሰገዱ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ራእይ 5