ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ራእይ 18:13-22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

13. ቀረፋ፣ ቅመም፣ ከርቤ፣ ቅባት፣ ዕጣን፣ የወይን ጠጅ፣ የወይራ ዘይት፣ የተሰለቀ ዱቄት፣ ስንዴ፣ ከብቶች፣ በጎች፣ ፈረሶች፣ ሠረገሎች፣ እንዲሁም ባሮችና የሰዎች ነፍሶች ነው።

14. እነርሱም፣ ‘የተመኘሽው ፍሬ ከአንቺ ርቆአል፤ ብልጽግናሽና ክብርሽ ሁሉ ጠፍቶአል፤ ዳግመኛም ተመልሶ አይመጣም” ይላሉ።

15. እነዚህን ነገሮች በመሸጥ በእርሷ የበለጸጉ ነጋዴዎች ሥቃይዋን ፈርተው በሩቅ ይቆማሉ፤ እነርሱም ያለቅሳሉ፤ ያዝናሉም፤

16. ድምፃቸውን ከፍ አድርገው እንዲህ ይላሉ፤“ቀጭን የተልባ እግር፣ ሐምራዊና ቀይ ልብስ የለበሰች፣በወርቅ፣ በከበረ ድንጋይና በዕንቍም ያጌጠች፣ታላቂቱ ከተማ ወዮላት! ወዮላት!

17. ያ ሁሉ ሀብት በአንድ ሰዓት ውስጥ ጠፋ።”“የመርከብ አዛዦች ሁሉ፣ በመርከብ የሚጓዙ መንገደኞች ሁሉ፣ የመርከብ ሠራተኞችና ኑሮአቸውን በባሕር ላይ የመሠረቱ ሁሉ በሩቅ ይቆማሉ።

18. እርሷ ስትቃጠል የሚወጣውን ጢስ ሲያዩ፣ ‘እንደዚች ያለ ታላቅ ከተማ ከቶ የት አለ?’ እያሉ ይጮኻሉ።

19. በራሳቸውም ላይ አቧራ ነስንሰው እያለ ቀሱና እያዘኑ እንዲህ ብለው ጮኹ፤“ ‘በባሕር ላይ መርከቦች ያላቸው ሁሉ፣በእርሷም ሀብት የበለጸጉ፣ለታላቂቱ ከተማ ወዮላት! ወዮላት!በአንድ ሰዓት ውስጥ ጠፍታለች።

20. ሰማይ ሆይ፤ በእርሷ ላይ ሐሤትአድርግ፤ቅዱሳን፣ ሐዋርያትና ነቢያትም ሐሤት አድርጉ፤በእናንተ ላይ ባደረሰችው ነገርእግዚአብሔር ፈርዶባታልና።’ ”

21. ከዚያም አንድ ብርቱ መልአክ፣ ትልቅ የወፍጮ ድንጋይ የሚመስል ድንጋይ አንሥቶ ወደ ባሕር ወረወረው፤ እንዲህም አለ፤“ታላቂቱ ከተማ ባቢሎን፣እንዲህ ባለ ኀይል ትወረወራለች፤ተመልሳም አትገኝም።

22. የበገና ደርዳሪዎችና የሙዚቀኞች ድምፅ፣የዋሽንትና የመለከት ነፊዎች ድምፅ፣ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይሰማም፤የእጅ ጥበብ ባለ ሙያ፣ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይገኝም፤የወፍጮ ድምፅም፣ዳግመኛ በአንቺ ውስጥ አይሰማም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ራእይ 18