ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ማርቆስ 8:7-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. እንዲሁም ትንንሽ ዓሣዎች ነበሯቸው፤ እርሱም ዓሣዎቹን ባርኮ እንዲያድሏቸው አዘዘ።

8. ሕዝቡም በልተው ጠገቡ፤ ከዚያም ደቀ መዛሙርቱ የተረፈውን ቍርስራሽ ሰባት መሶብ ሙሉ አነሡ።

9. በዚያም አራት ሺህ ያህል ሰዎች ነበሩ፤ ካሰናበታቸውም በኋላ፣

10. ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ዳልማኑታ ወደተባለ ስፍራ ሄደ።

11. ፈሪሳውያንም ወጥተው ከኢየሱስ ጋር ይከራከሩ ጀመር። ሊፈትኑትም ፈልገው ከሰማይ ምልክት እንዲያሳያቸው ጠየቁት።

12. እርሱም በመንፈሱ እጅግ በመቃተት፣ “ይህ ትውልድ ምልክት የሚፈልገው ለምንድን ነው? እውነት እላችኋለሁ፤ ለዚህ ትውልድ ምንም ምልክት አይሰጠውም!” አለ።

13. ከዚያም ትቶአቸው በጀልባ ወደ ማዶ ተሻገረ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ማርቆስ 8