ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሐዋርያት ሥራ 2:26-35 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

26. ስለዚህ ልቤ ደስ አለው፤ አንደበቴም ሐሤት አደረገ፤ሥጋዬም በተስፋ ይኖራል።

27. ነፍሴን በሲኦል አትተዋትምና፤ቅዱስህም መበስበስን እንዲያይ አታደርግም።

28. የሕይወትን መንገድ እንዳውቅ አደረግኸኝ፤በፊትህም በሐሤት ትሞላኛለህ።’

29. “ወንድሞች ሆይ፤ ከቀደምት አባቶች ዳዊት ሞቶ እንደ ተቀበረ፣ መቃብሩም እስከ ዛሬ ድረስ በመካከላችን እንደሚገኝ በድፍረት መናገር እችላለሁ።

30. ነቢይ በመሆኑም፣ እግዚአብሔር ከዘሮቹ አንዱን በዙፋኑ ላይ እንደሚያስቀምጥ በመሐላ ቃል የገባለት መሆኑን ዐወቀ።

31. ይህንን አስቀድሞ በማየቱ እርሱ በሲኦል እንደማይቀርና ሥጋውም እንደማይበሰብስ ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ ተናገረ።

32. ይህን ኢየሱስ፣ እግዚአብሔር ከሞት አስነሣው፤ እኛም ሁላችን ለዚህ ነገር ምስክሮች ነን።

33. ስለዚህ በእግዚአብሔር ቀኝ ከፍ ከፍ ካለ በኋላ፣ የመንፈስ ቅዱስን ተስፋ ከአብ ተቀብሎ አሁን የምታዩትንና የምትሰሙትን አፈሰሰው።

34. ዳዊት ወደ ሰማያት አልወጣም፤እርሱ ራሱ ግን እንዲህ ብሎአል፤“ ‘ጌታ ጌታዬን፣

35. “ጠላቶችህን ለእግርህ መረገጫ እስከማደርግልህ ድረስ፣በቀኜ ተቀመጥ” አለው።’

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሐዋርያት ሥራ 2