ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሐዋርያት ሥራ 15:37-41 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

37. በርናባስም ማርቆስ የተባለው ዮሐንስ አብሮአችው እንዲሄድ ፈለገ፤

38. ጳውሎስ ግን እርሱን ይዞ ለመሄድ አልፈለገም፤ ምክንያቱም፣ ቀደም ሲል ማርቆስ ከእነርሱ ተለይቶ በጵንፍልያ ስለ ቀረና ወደ ሥራ አብሮአቸው ስላልሄደ ነበር።

39. እንዲህ የከረረ አለመግባባት በመካከላቸው ስለ ተፈጠረ እርስ በርስ ተለያዩ፤ ስለዚህ በርናባስ ማርቆስን ይዞ በመርከብ ወደ ቆጵሮስ ሄደ።

40. ጳውሎስ ግን ሲላስን መረጠ፤ ወንድሞችም ለጌታ ጸጋ ዐደራ ከሰጡት በኋላ ተለይቶአቸው ሄደ፤

41. አብያተ ክርስቲያናትንም እያበረታታ በሶርያና በኪልቅያ በኩል ዐለፈ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሐዋርያት ሥራ 15