ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሉቃስ 4:9-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. ከዚያም ወደ ኢየሩሳሌም ወስዶ በቤተ መቅደስ ጒልላት ላይ አቆመውና እንዲህ አለው፤ “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፣ እስቲ ራስህን ከዚህ ወደ ታች ወርውር፤

10. ምክንያቱም እንዲህ ተብሎ ተጽፎአል፤“ ‘ይጠብቁህ ዘንድ፣መላእክቱን ስለ አንተ ያዛቸዋል፤

11. እግርህም ከድንጋይ ጋር እንዳይጋጭ፣በእጆቻቸው ወደ ላይ አንሥተው ይይዙሃል።’ ”

12. ኢየሱስም፣ “ ‘ጌታ አምላክህን አትፈታተነው’ ተብሎአል” ብሎ መለሰለት።

13. ዲያብሎስም ፈተናውን ሁሉ ከጨረሰ በኋላ ሌላ አመቺ ጊዜ እስኪያገኝ ድረስ ከእርሱ ተለየ።

14. ኢየሱስም በመንፈስ ኀይል ወደ ገሊላ ተመለሰ፤ ዝናውም በአካባቢው ባለው አገር ሁሉ ወጣ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሉቃስ 4