ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሉቃስ 4:3-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. ዲያብሎስም፣ “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፣ እስቲ ይህ ድንጋይ እንጀራ እንዲሆን እዘዘው” አለው።

4. ኢየሱስም፣ “ ‘ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም’ ተብሎ ተጽፎአል” ብሎ መለሰለት።

5. ከዚያም ዲያብሎስ ወደ አንድ ከፍታ ቦታ አውጥቶት የዓለምን መንግሥታት ሁሉ በቅጽበት አሳየው፤

6. እንዲህም አለው፤ “የእነዚህ መንግሥታት ሥልጣንና ክብር ሁሉ ለእኔ ተሰጥቶአል፤ እኔም ለምወደው ስለምሰጥ፣ ለአንተ እሰጥሃለሁ፤

7. ስለዚህ ብትሰግድልኝ ይህ ሁሉ የአንተ ይሆናል።”

8. ኢየሱስም መልሶ፣ “ ‘ለጌታ ለአምላክህ ስገድ፤ እርሱንም ብቻ አምልክ’ ተብሎ ተጽፎአል” አለው።

9. ከዚያም ወደ ኢየሩሳሌም ወስዶ በቤተ መቅደስ ጒልላት ላይ አቆመውና እንዲህ አለው፤ “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፣ እስቲ ራስህን ከዚህ ወደ ታች ወርውር፤

10. ምክንያቱም እንዲህ ተብሎ ተጽፎአል፤“ ‘ይጠብቁህ ዘንድ፣መላእክቱን ስለ አንተ ያዛቸዋል፤

11. እግርህም ከድንጋይ ጋር እንዳይጋጭ፣በእጆቻቸው ወደ ላይ አንሥተው ይይዙሃል።’ ”

12. ኢየሱስም፣ “ ‘ጌታ አምላክህን አትፈታተነው’ ተብሎአል” ብሎ መለሰለት።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሉቃስ 4