ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሉቃስ 18:40-43 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

40. ኢየሱስም ቆም ብሎ ሰውየውን ወደ እርሱ እንዲያመጡት አዘዘ፤ ወደ እርሱም በቀረበ ጊዜ፣

41. “ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ?” ብሎ ጠየቀው።ዐይነ ስውሩም፣ “ጌታ ሆይ፤ ማየት እፈልጋለሁ” አለው።

42. ኢየሱስም፣ “እይ፤ እምነትህ አድኖሃል” አለው።

43. ሰውየውም ወዲያውኑ ማየት ቻለ፤ እግዚአብሔርንም እያከበረ ኢየሱስን ተከተለው። ሕዝቡም ሁሉ ይህን ሲያዩ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሉቃስ 18