ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 5:8-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. ሴት በአጠቃላይ 912 ዓመት ከኖረ በኋላ ሞተ።

9. ሄኖስ፣ ዕድሜው 90 ዓመት በሆነ ጊዜ ቃይናንን ወለደ፤

10. ሄኖስ ቃይናንን ከወለደ በኋላ 815 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችንም ወለደ።

11. ሄኖስ በአጠቃላይ 905 ዓመት ከኖረ በኋላ ሞተ።

12. ቃይናን፣ ዕድሜው 70 ዓመት ሲሆን መላልኤልን ወለደ፤

13. ቃይናን መላልኤልን ከወለደ በኋላ 840 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችንም ወለደ።

14. ቃይናን በአጠቃላይ 910 ዓመት ከኖረ በኋላ ሞተ።

15. መላልኤል፣ ዕድሜው 65 ዓመት በሆነ ጊዜ ያሬድን ወለደ፤

16. መላልኤል ያሬድን ከወለደ በኋላ 830 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችንም ወለደ።

17. መላልኤል በአጠቃላይ 895 ዓመት ከኖረ በኋላ ሞተ።

18. ያሬድ፣ ዕድሜው 162 ዓመት ሲሆን ሄኖክን ወለደ፤

19. ያሬድ ሄኖክን ከወለደ በኋላ 800 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችንም ወለደ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 5