ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 5:5-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. አዳም በአጠቃላይ 930 ዓመት ከኖረ በኋላ ሞተ።

6. ሴት፣ ዕድሜው 105 ዓመት ሲሆን ሄኖስን ወለደ፤

7. ሴት ሄኖስን ከወለደ በኋላ 807 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችንም ወለደ።

8. ሴት በአጠቃላይ 912 ዓመት ከኖረ በኋላ ሞተ።

9. ሄኖስ፣ ዕድሜው 90 ዓመት በሆነ ጊዜ ቃይናንን ወለደ፤

10. ሄኖስ ቃይናንን ከወለደ በኋላ 815 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችንም ወለደ።

11. ሄኖስ በአጠቃላይ 905 ዓመት ከኖረ በኋላ ሞተ።

12. ቃይናን፣ ዕድሜው 70 ዓመት ሲሆን መላልኤልን ወለደ፤

13. ቃይናን መላልኤልን ከወለደ በኋላ 840 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችንም ወለደ።

14. ቃይናን በአጠቃላይ 910 ዓመት ከኖረ በኋላ ሞተ።

15. መላልኤል፣ ዕድሜው 65 ዓመት በሆነ ጊዜ ያሬድን ወለደ፤

16. መላልኤል ያሬድን ከወለደ በኋላ 830 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችንም ወለደ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 5