ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፀአት 26:15-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

15. “ለማደሪያው ድንኳን ከግራር ዕንጨት ወጋግራዎችን አብጅ።

16. እያንዳንዱም ወጋግራ ርዝመቱ ዐሥር ክንድ ወርዱም አንድ ክንድ ተኵል ይሁን፤

17. ሁለት ጉጦችም ጎን ለጎን ይሁኑለት፤ የማደሪያውን ድንኳን ወጋግራዎች ሁሉ በዚሁ መልክ አብጅ

18. ለማደሪያው ድንኳን ክፍል ሃያ ወጋግራዎችን ሥራ።

19. ከሥራቸው የሚሆኑ አርባ የብር መቆሚያዎችን አብጅ፤ በእያንዳንዱ ጒጠት ሥር አንድ መቆሚያ ሲሆን፣ ለእያንዳንዱም ወጋግራ ሁለት መቆሚያዎች ይኑሩ።

20. በሌላው ጎን፣ ከማደሪያው ድንኳን በስተ ሰሜን በኩል ሃያ ወጋግራዎችን አብጅ፤

21. በእያንዳንዱም ወጋግራ ሥር ሁለት ሁለት መቆሚያ ሆኖ አርባ የብር መቆሚያዎችን አብጅ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፀአት 26