ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፀአት 23:11-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

11. ነገር ግን በሰባተኛው ዓመት ምድሪቱን ሳትጠቀምባትና ሳታርሳት እንዲሁ ተዋት፤ ከዚያም በወገንህ መካከል ያሉት ድኾች ከእርሷ ምግብ ያገኛሉ፤ የዱር አራዊትም ከእነርሱ የተረፈውን ይበላሉ። በወይን ቦታህና በወይራ ዛፎችህም ላይ እንዲሁ አድርግ።

12. “ስድስት ቀን ሥራህን ሥራ፤ በሬህና አህያህ በቤትህ የተወለደው ባሪያና መጻተኛው ያርፉ ዘንድ በሰባተኛው ቀን ምንም አትሥራ።

13. ያልኋችሁን ሁሉ ታደርጉ ዘንድ ተጠንቀቁ፤ የሌሎችን አማልክት ስም አትጥሩ፤ ከአፋችሁም አይስሙ።

14. በዓመት ሦስት ጊዜ ለእኔ በዓልን ታከብራላችሁ።

15. “ያልቦካ የቂጣ በዓልን አክብር፤ እንዳዘዝኩህ ሰባት ቀን እርሾ የሌለውን ቂጣ ብላ፤ ይህንንም በአቢብ ወር በተወሰነ ቀን አድርግ፤ በዚያ ወር ከግብፅ ወጥተሃልና።“ማንም በፊቴ ባዶ እጁን አይቅረብ።

16. “በማሳህ ላይ በዘራኸው እህል በኵራት የመከርን በዓል አክብር።“በዓመቱ መጨረሻ በማሳህ ላይ ያለውን እህልህን ስትሰበስብ የመክተቻውን በዓል አክብር።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፀአት 23