ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘካርያስ 13:4-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. “በዚያን ቀን እያንዳንዱ ነቢይ ስለሚናገረው የትንቢት ራእይ ያፍራል፤ ለማታለልም የነቢያትን ጠጒራም ልብስ አይለብስም።

5. እርሱም፣ ‘እኔ ገበሬ እንጂ ነቢይ አይደለሁም፤ ከልጅነቴ ጀምሮ ኑሮዬ የተመሠረተውም በዕርሻ ላይ ነው’ ይላል።

6. አንድ ሰው፣ ‘ይህ በሰውነትህ ላይ ያለው ቊስል ምንድን ነው?’ ብሎ ቢጠይቀው፣ ‘በባልንጀሮቼ ቤት ሳለሁ የቈሰልሁት ነው’ ይላል።

7. እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤“ሰይፍ ሆይ፤ በእረኛዬ፣በቅርብ ወዳጄ ላይ ንቃ!እረኛውን ምታ፤በጎቹ ይበተናሉ፤እኔም ክንዴን ወደ ታናናሾቹ አዞራለሁ።

8. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “የምድር ሁሉ፣ሁለት ሦስተኛው ተመትቶ ይጠፋል፤አንድ ሦስተኛው ግን በውስጡ ይቀራል፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘካርያስ 13