ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 27:7-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. “የሰለጰዓድ ልጆች ጥያቄ ትክክል ነው፤ በእርግጥ በአባታቸው ዘመዶች መካከል ድርሻቸውን ርስት አድርገህ ልትሰጣቸው ስለሚገባ የአባታቸውን ድርሻ ለእነርሱ አስተላልፍላቸው።

8. “እስራኤላውያንን እንዲህ በላቸው፤ ‘አንድ ሰው ወንድ ልጅ ሳይተካ ቢሞት ውርሱን ለሴት ልጁ አስተላልፉ።

9. ሴት ልጅ ከሌለችው ደግሞ ውርሱን ለወንድሞቹ ስጡ።

10. ወንድሞች ከሌሉትም ውርሱን ለአባቱ ወንድሞች ስጡ።

11. አባቱ ወንድሞች ከሌሉትውርሱ ከጐሣው መካከል ቅርብ ለሆነ ዘመዱ ይሰጥ፤ እርሱም ይውረሰው። ይህም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን ባዘዘው መሠረት ለእስራኤላውያን ሕጋዊ መመሪያ ይሆናቸዋል።’ ”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 27