ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 26:33-49 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

33. የኦፌር ልጅ ሰለጰዓድ ወንዶች ልጆች አልነበሩትም፤ ልጆቹ ሴቶች ብቻ ነበሩ፤ እነርሱም ማህለህ፣ ኑዓ፣ ዔግላ፣ ሚልካና ቲርጻ ይባላሉ።

34. እነዚህ የምናሴ ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህ የተቈጠሩት አምሳ ሁለት ሺህ ሰባት መቶ ነበሩ።

35. የኤፍሬም ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በሱቱላ በኩል፣ የሱቱላውያን ጐሣ፣በቤኬር በኩል፣ የቤኬራውያን ጐሣ፣በታሐን በኩል፣ የታሐናውያን ጐሣ፤

36. የሱቱላ ዘሮች እነዚህ ነበሩ፤በዔዴን በኩል፣ የዔዴውናውያን ጐሣ፤

37. እነዚህ የኤፍሬም ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህ የተቈጠሩት ሠላሳ ሁለት ሺህ አምስት መቶ ነበሩ።እነዚህም በየጐሣቸው የተቈጠሩ የዮሴፍ ዘሮች ነበሩ።

38. የብንያም ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በቤላ በኩል፣ የቤላውያን ጐሣ፣በአስቤል በኩል፣ የአስቤላውያን ጐሣ፣በአኪራን በኩል፣ የአኪራናውያን ጐሣ፣

39. በሶፋን በኩል፣ የሶፋናውያን ጐሣ፣በሑፋም በኩል፣ የሑፋማውያን ጐሣ፤

40. የቤላ ዘሮች በአርድና በናዕማን በኩል፤በአርድ በኩል፣ የአርዳውያን ጐሣ፣በናዕማን በኩል፣ የናዕማናውያን ጐሣ፤

41. እነዚህ የብንያም ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህም የተቈጠሩት አርባ አምስት ሺህ ስድስት መቶ ነበሩ።

42. የዳን ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በስምዔ በኩል፣ የሰምዔያውያን ጐሣዎች።እነዚህ እንግዲህ የዳን ጐሣዎች ሲሆኑ፣

43. ሁሉም የሰምዔያውያን ጐሣዎች ነበሩ፤ ከእነዚህ የተቈጠሩት ደግሞ ሥልሳ አራት ሺህ አራት መቶ ነበሩ።

44. የአሴር ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በዩምና በኩል፣ የዩምናውያን ጐሣ፣በየሱዋ በኩል፣ የየሱዋውያን ጐሣ፣በበሪዓ በኩል፣ የበሪዓውያን ጐሣ፤

45. እንዲሁም በበሪዓ ዘሮች በኩል፣በሔቤር በኩል፣ የሔቤራውያን ጐሣ፣በመልኪኤል በኩል፣ የመልኪኤላውያን ጐሣ።

46. አሴር ሤራሕ የምትባል ልጅ ነበረችው።

47. እነዚህ የአሴር ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህ የተቈጠሩት አምሳ ሦስት ሺህ አራት መቶ ነበሩ።

48. የንፍታሌም ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በያሕጽኤል በኩል፣ የያሕጽኤላውያን ጐሣ፣በጉኒ በኩል፣ የጉናውያን ጐሣ፣

49. በሺሌም በኩል፣ የሺሌማውያን ጐሣ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 26