ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 26:27-42 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

27. እነዚህ የዛብሎን ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህ የተቈጠሩት ሥልሳ ሺህ አምስት መቶ ነበሩ።

28. የዮሴፍ ዘሮች በምናሴና በኤፍሬም በኩል ያሉት በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤

29. የምናሴ ዘሮች፤በማኪር በኩል፣ የማኪራውያን ጐሣ፤ ማኪርም የገለዓድ አባት ነው፤በገለዓድ በኩል፣ የገለዓዳውያን ጐሣ፤

30. የገለዓድ ዘሮች እነዚህ ነበሩ፤በኢዔዝር በኩል፣ የኢዓዝራውያን ጐሣ፣በኬሌግ በኩል፣ የኬሌጋውያን ጐሣ፣

31. በአሥሪኤል በኩል፣ የአሥሪኤላውያን ጐሣ፣በሴኬም በኩል፣ የሴኬማውያን ጐሣ፣

32. በሸሚዳ በኩል፣ የሸሚዳውያን ጐሣ፣በኦፌር በኩል፣ የኦፌራውያን ጐሣ፣

33. የኦፌር ልጅ ሰለጰዓድ ወንዶች ልጆች አልነበሩትም፤ ልጆቹ ሴቶች ብቻ ነበሩ፤ እነርሱም ማህለህ፣ ኑዓ፣ ዔግላ፣ ሚልካና ቲርጻ ይባላሉ።

34. እነዚህ የምናሴ ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህ የተቈጠሩት አምሳ ሁለት ሺህ ሰባት መቶ ነበሩ።

35. የኤፍሬም ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በሱቱላ በኩል፣ የሱቱላውያን ጐሣ፣በቤኬር በኩል፣ የቤኬራውያን ጐሣ፣በታሐን በኩል፣ የታሐናውያን ጐሣ፤

36. የሱቱላ ዘሮች እነዚህ ነበሩ፤በዔዴን በኩል፣ የዔዴውናውያን ጐሣ፤

37. እነዚህ የኤፍሬም ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህ የተቈጠሩት ሠላሳ ሁለት ሺህ አምስት መቶ ነበሩ።እነዚህም በየጐሣቸው የተቈጠሩ የዮሴፍ ዘሮች ነበሩ።

38. የብንያም ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በቤላ በኩል፣ የቤላውያን ጐሣ፣በአስቤል በኩል፣ የአስቤላውያን ጐሣ፣በአኪራን በኩል፣ የአኪራናውያን ጐሣ፣

39. በሶፋን በኩል፣ የሶፋናውያን ጐሣ፣በሑፋም በኩል፣ የሑፋማውያን ጐሣ፤

40. የቤላ ዘሮች በአርድና በናዕማን በኩል፤በአርድ በኩል፣ የአርዳውያን ጐሣ፣በናዕማን በኩል፣ የናዕማናውያን ጐሣ፤

41. እነዚህ የብንያም ጐሣዎች ሲሆኑ፣ ከእነዚህም የተቈጠሩት አርባ አምስት ሺህ ስድስት መቶ ነበሩ።

42. የዳን ዘሮች በየጐሣቸው እነዚህ ነበሩ፤በስምዔ በኩል፣ የሰምዔያውያን ጐሣዎች።እነዚህ እንግዲህ የዳን ጐሣዎች ሲሆኑ፣

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 26