ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 13:1-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤

2. “ለእስራኤላውያን የምሰጠውን የከነዓንን ምድር እንዲሰልሉ ጥቂት ሰዎች ላክ፤ ከእያንዳንዱም የአባቶች ነገድ አለቃ ይላክ።”

3. ስለዚህ ሙሴ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ትእዛዝ ከፋራን ምድረ በዳ እነዚህን ላካቸው፤ ሁሉም የእስራኤላውያን አለቆች ነበሩ፤

4. ስማቸውም እንደሚከተለው ነው፤ከሮቤል ነገድ፣ የዘኩር ልጅ ሳሙኤል፤

5. ከስምዖን ነገድ፣ የሱሬ ልጅ ሰፈጥ፤

6. ከይሁዳ ነገድ፣ የዩፎኒ ልጅ ካሌብ፤

7. ከይሳኮር ነገድ፣ የዮሴፍ ልጅ ይግአል፤

8. ከኤፍሬም ነገድ፣ የነዌ ልጅ አውሴ፤

9. ከብንያም ነገድ፣ የራፉ ልጅ ፈልጢ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 13