ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 1:25-32 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

25. ከጋድ ነገድ የተቈጠሩትም አርባ አምስት ሺህ ስድስት መቶ አምሳ ነበሩ።

26. ከይሁዳ ዝርያ፦ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ።

27. ከይሁዳ ነገድ የተቈጠሩትም ሰባ አራት ሺህ ስድስት መቶ ነበሩ።

28. ከይሳኮር ዝርያ፦ዕድሜአቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ።

29. ከይሳኮር ነገድ የተቈጠሩትም አምሳ አራት ሺህ አራት መቶ ነበሩ።

30. ከዛብሎን ዝርያ፦ዕድሜያቸው ሃያ አመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና፣ በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ።

31. ከዛብሎን ነገድ የተቈጠሩትም አምሳ ሰባት ሺህ አራት መቶ ነበሩ።

32. ከዮሴፍ ልጆች፦ከኤፍሬም ዝርያ ዕድሜያቸው ሃያ ዓመትና ከዚያም በላይ ሆኖ ለመዋጋት ብቁ የሆኑት ወንዶች ሁሉ በየጐሣቸውና በየቤተ ሰባቸው መዝገብ መሠረት ስማቸው አንድ በአንድ ተጻፈ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 1