ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዕንባቆም 1:3-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. ስለ ምን በደልን እንዳይ አደረግኸኝ?እንዴትስ ግፍ ሲፈጸም ትታገሣለህ?ጥፋትና ግፍ በፊቴ አለ፤ጠብና ግጭት በዝቶአል።

4. ስለዚህ ሕግ ላልቶአል፤ፍትሕ ድል አይነሣም፤ፍትሕ ይጣመም ዘንድ፣ክፉዎች ጻድቃንን ይከባሉ።

5. “ቢነገራችሁም እንኳ፣የማታምኑትን እናንተን፣በዘመናችሁ አንድ ነገር ስለማደርግ፣እነሆ፤ ሕዝቡን እዩ፤ ተመልከቱም፤እጅግም ተደነቁ።

6. የራሳቸው ያልሆኑትን መኖሪያ ስፍራዎች ለመያዝ፣ምድርን ሁሉ የሚወሩትን፣ጨካኝና ፈጣን የሆኑትን፣ባቢሎናውያንን አስነሣለሁ።

7. እነርሱም የሚያስፈሩና የሚያስደነግጡ ናቸው፤ፍርዳቸውና ክብራቸው፣ከራሳቸው ይወጣል።

8. ፈረሶቻቸው ከነብር ይልቅ ፈጣኖች፣ከማታም ተኵላ ይልቅ ጨካኞች ናቸው።ፈረሰኞቻቸው በፍጥነት ይጋልባሉ፤ከሩቅ ስፍራም ይመጣሉ።ነጥቆ ለመብላት እንደሚቸኵል አሞራ ይበራሉ፤

9. ሁሉም ለዐመፅ ታጥቀው ይመጣሉ።ሰራዊታቸው እንደ ምድረ በዳ ነፋስ ወደ ፊት ይገሠግሣል፤ምርኮኞችንም እንደ አሸዋ ይሰበስባል።

10. ነገሥታትን ይንቃል፤በገዦችም ላይ ያፌዛል፤በምሽግ ሁሉ ላይ ይሥቃል፤የዐፈር ቊልል ሠርቶም ይይዘዋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዕንባቆም 1