ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 6:2-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. ውብና ሽሙንሙን የሆነችዋን፣የጽዮንን ሴት ልጅ አጠፋታለሁ።

3. እረኞች መንጎቻቸውን ይዘው ይመጡባታል፤ድንኳናቸውን በዙሪያዋ ይተክላሉ፤እያንዳንዳቸውም በየአቅጣጫቸው መንጋቸውን ያሰማራሉ።”

4. “በእርሷ ላይ ጦርነት ዐውጁ፤ተነሡ በቀትር አደጋ እንጣልባት፤ወይ ጉድ! ቀኑ እኮ መሸብን!ጥላው ረዘመ።

5. እንግዲህ ተነሡ በሌሊት እናጥቃት፤ምሽጎቿንም እንደምስስ!”

6. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ዛፎቹን ቍረጡ፤በኢየሩሳሌም ዙሪያ የዐፈር ድልድል ሥሩ።ይህቺ ከተማ ቅጣት ይገባታል፤ግፍን ተሞልታለችና።

7. የውሃ ጒድጓድ ውሃ እንደሚያመነጭ፣እርሷም እንዲሁ ክፋቷን ታፈልቃለች።ዐመፅና ጥፋት በውስጧ ይስተጋባል፤ሕመሟና ቍስሏ ዘወትር ይታየኛል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 6