ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 6:1-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. “እናንት የብንያም ልጆች፤ ክፉ ነገር፣ታላቅም ጥፋት ከሰሜን ድንገት ይመጣልና፣ከኢየሩሳሌም ሸሽታችሁ አምልጡ፤በቴቁሔ መለከትን ንፉ፤በቤትሐካሪም ላይ ምልክት ከፍአድርጋችሁ አሳዩ።

2. ውብና ሽሙንሙን የሆነችዋን፣የጽዮንን ሴት ልጅ አጠፋታለሁ።

3. እረኞች መንጎቻቸውን ይዘው ይመጡባታል፤ድንኳናቸውን በዙሪያዋ ይተክላሉ፤እያንዳንዳቸውም በየአቅጣጫቸው መንጋቸውን ያሰማራሉ።”

4. “በእርሷ ላይ ጦርነት ዐውጁ፤ተነሡ በቀትር አደጋ እንጣልባት፤ወይ ጉድ! ቀኑ እኮ መሸብን!ጥላው ረዘመ።

5. እንግዲህ ተነሡ በሌሊት እናጥቃት፤ምሽጎቿንም እንደምስስ!”

6. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ዛፎቹን ቍረጡ፤በኢየሩሳሌም ዙሪያ የዐፈር ድልድል ሥሩ።ይህቺ ከተማ ቅጣት ይገባታል፤ግፍን ተሞልታለችና።

7. የውሃ ጒድጓድ ውሃ እንደሚያመነጭ፣እርሷም እንዲሁ ክፋቷን ታፈልቃለች።ዐመፅና ጥፋት በውስጧ ይስተጋባል፤ሕመሟና ቍስሏ ዘወትር ይታየኛል።

8. ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ተጠንቀቂ፤አለበለዚያ ከአንቺ ዘወር እላለሁ፤ማንም ሊኖርባት እስከማይችል ድረስ፣ምድርሽን ባዶ አደርጋለሁ።”

9. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“የወይን ፍሬ ተሟጦ እንደሚቃረም፣ከእስራኤል የተረፉትን እንዲሁ ይቃርሟቸው።ወይን ለቃሚ እንደሚለቅም፣እጅህን ወደ ቅርንጫፎቹ ደጋግመህ ዘርጋ።”

10. ለማን ልናገር? ማንን ላስጠንቅቅ?ማንስ ይሰማኛል?እነሆ፣ ጆሮዎቻቸው አልተገረዙምና፣መስማት አይችሉም። በእግዚአብሔር ቃል ይሣለቃሉ፤ደስም አይሰኙበትም።

11. በእነርሱ ላይ በእግዚአብሔር ቍጣ ተሞልቻለሁ፤በውስጤም ልይዘው አልቻልሁም።“መንገድ ላይ በሚገኙ ሕፃናት፣በተሰበሰቡ ወጣቶችም ላይ አፍስሰው፤ባልም ሚስትም፣ያረጁና የጃጁም አያመልጡም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 6