ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 50:28-35 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

28. እግዚአብሔር አምላካችን የተበቀለውን፣ስለ ቤተ መቅደሱ የተበቀለውን በቀል፣ከባቢሎን የመጡ ኰብላዮችና ስደተኞች፣በጽዮን የሚናገሩትን ስሟቸው።

29. “ቀስት የሚገትሩትን፣ቀስተኞችን ሁሉ በባቢሎን ላይ ጥሩ፤አንድም ሰው እንዳያመልጥ፣ዙሪያውን ሁሉ መሽጉ፤የእስራኤልን ቅዱስ፣ እግዚአብሔርን አቃላለችና፣እንደ ሥራዋ መጠን መልሱላት፤በሌሎች ላይ እንዳደረገችውም አድርጉባት።

30. ስለዚህ ወንዶች ወጣቶቿ በየአደባባዩ ይረግፋሉ፤በዚያ ቀን ወታደሮቿ ሁሉ ይወድቃሉ፤”ይላል እግዚአብሔር፤

31. “አንተ ትዕቢተኛ፤ እነሆ፣ በአንተ ላይ ተነሥቻለሁ፤”ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤“የምትቀጣበት ጊዜ፣ቀንህ ደርሶአልና።

32. ትዕቢተኛው ይሰናከላል፤ ይወድቃልም፤የሚያነሣውም የለም፤በዙሪያው ያሉትን ሁሉ የሚበላ እሳት፣በከተሞቹ ውስጥ አስነሣለሁ።”

33. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“የእስራኤል ሕዝብና የይሁዳ ሕዝብ፣በአንድነት ተጨቍነዋል፤የማረኳቸውም ሁሉ አጥብቀው ይዘዋቸዋል፤ይለቅቋቸውም ዘንድ እንቢ ብለዋል።

34. ነገር ግን ቤዛቸው ብርቱ ነው፤ስሙም የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው፤ለምድራቸው ዕረፍትን ለመስጠት፤ተግቶ ይሟገትላቸዋል፤በባቢሎን የሚኖሩትን ግን ዕረፍት ይነሣቸዋል።

35. “ሰይፍ በባቢሎናውያን ላይ መጣ!”ይላል እግዚአብሔር፤“በባቢሎን ነዋሪዎች ላይ፤በባለ ሥልጣኖቿና በጥበበኞቿም ላይ ተመዘዘ!

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 50