ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 50:1-5 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር ስለ ባቢሎንና ስለ ባቢሎናውያን ምድር፣ በነቢዩ ኤርምያስ በኩል የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

2. “በሕዝቦች መካከል ተናገሩ፤ አስታውቁም፤ሰንደቅ ዐላማ አንሡ፤ ዐውጁ፤አንዳች ሳታስቀሩ፣ እንዲህ በሉ፤‘ባቢሎን ትያዛለች፤ቤል ይዋረዳል፤ሜሮዳክ በሽብር ይሞላል፤ጣዖቶቿ ይዋረዳሉ፤አማልክቷም ይሸበራሉ።’

3. ከሰሜን አንድ መንግሥት መጥቶ ይወጋታል፤ምድሯንም ባድማ ያደርጋል፤የሚኖርባትም አይገኝም፤ሰዎችና እንስሳትም ሸሽተው ይሄዳሉ።

4. “በዚያ ዘመን፣ በዚያ ጊዜም፤”ይላል እግዚአብሔር፤“የእስራኤል ሕዝብና የይሁዳ ሕዝብ በአንድነት ይመጣሉ፤አምላካቸውንም እግዚአብሔርን በመፈለግ እያለቀሱ ይመጣሉ።

5. ወደ ጽዮን የሚወስደውን መንገድ ይጠይቃሉ፤ፊታቸውንም ወደዚያ ያቀናሉ።መጥተውም ከቶ በማይረሳ፣በዘላለም ቃል ኪዳን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ይጣበቃሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 50