ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 48:25-40 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

25. የሞዓብ ቀንድ ተቈርጦአል፤እጁም ተሰባብሮአል፤”ይላል እግዚአብሔር።

26. “እግዚአብሔርን ንቆአልና፣ሞዓብን በመጠጥ አስክሩት።ሞዓብ በትፋቱ ላይ ይንከባለል፤ለመዘባበቻም ይሁን።

27. በእስራኤል ላይ ስታላግጥ አልነበረምን?ስለ እርሷ በተናገርህ ቍጥር፣እያቃለልሃት ራስህን የምትነቀንቀውስ፣ከሌቦች ጋር ስትሰርቅ ተይዛለችን?

28. እናንተ በሞዓብ የምትኖሩ ሆይ፤ከከተማ ወጥታችሁ በዐለት መካከል ኑሩ፤በገደል አፋፍ ላይ ጐጆዋን እንደምትሠራ፣እንደ ርግብ ሁኑ።

29. “ስለ ሞዓብ ትዕቢት፣ስለ እብሪቱና ስለ ኵራቱ፣ስለ ትምክሕቱና ስለ መጓደዱ፣ስለ ልቡም ማበጥ ሰምተናል።

30. መዳፉን ዐውቃለሁ፤ ነገር ግን ከንቱ ነው፤”ይላል እግዚአብሔር።“ጒራውም ፋይዳ አይኖረውም።

31. ስለዚህ ለሞዓብ አለቅሳለሁ፤ለሞዓብ ምድር ሁሉ ዋይ እላለሁ፤ለቂርሔሬስ ሰዎችም የልቅሶ ድምፅ አሰማለሁ።

32. የሴባማ ወይን ሆይ፤ለኢያዜር ካለቀስሁት እንኳ ይልቅ አለቅስልሻለሁ፤ቅርንጫፎችሽ እስከ ባሕሩ ተዘርግተዋል፤እስከ ኢያዜርም ደርሰዋል፤ለመከር በደረሰው ፍሬሽና በወይንሽ ላይ፣አጥፊው መጥቶአል።

33. ከሞዓብ የአትክልት ቦታና እርሻ፣ሐሤትና ደስታ ርቆአል፤የወይን ጠጅ ከመጭመቂያው እንዳይወርድ አድርቄዋለሁ፤በእልልታ የሚጨምቀውም አይገኝም፤በዚያ ድምፅ ቢሰማም፣የእልልታ ድምፅ አይደለም።

34. “ከሐሴቦን እስከ ኤልያሊና እስከ ያሀጽ፣ከዞዓር እስከ ሖሮናይም፣ እስከ ዔግላት ሺሊሺያ ድረስ፣ጩኸታቸው ከፍ ብሎ ይሰማል፤የኔሞሬም ውሃ እንኳ ደርቆአልና።

35. በመስገጃ ኰረብቶች ላይ የሚሠዉትን፣ለአማልክታቸው የሚያጥኑትን፣ከሞዓብ አጠፋለሁ፤”ይላል እግዚአብሔር፤

36. “ስለዚህ ልቤ ለሞዓብ እንደ ዋሽንት ያንጐራጒራል፤ለቂርሔሬስ ሰዎችም እንደ ዋሽንት ያንጐራጒራል።ያከማቹት ንብረት ጠፍቶአልና።

37. የእያንዳንዱ ሰው ራስ፣ጢምም ሁሉ ተላጭቶአል፤እጅ ሁሉ ተቸፍችፎአል፤ወገብም ሁሉ ማቅ ታጥቆአል።

38. በሞዓብ ቤቶች ጣራ ሁሉ ላይ፤፣በሕዝብም አደባባዮች፣ሐዘን እንጂ ሌላ የለም፤እንደማይፈለግ እንስራ፣ሞዓብን ሰብሬአለሁና፤”ይላል እግዚአብሔር።

39. “እንዴት ተንኰታኰተ! ምንኛስ አለቀሱ!ሞዓብ እንዴት ዐፍሮ ጀርባውን አዞረ!ሞዓብ የመሰደቢያ፣በዙሪያው ላሉትም ሁሉ የሽብር ምልክት ሆነ።”

40. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነሆ፤ እንደ ንስር ተወርውሮ ይወርድበታል፤ክንፎቹንም በሞዓብ ላይ ይዘረጋል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 48