ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 31:8-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. እነሆ፤ ከሰሜን ምድር አመጣቸዋለሁ፤ከምድርም ዳርቻ እሰበስባቸዋለሁ፤በመካከላቸውም ዕውሮችና አንካሶች፣ነፍሰ ጡርና በምጥ ላይ ያሉ ሴቶች ይገኛሉ፤ታላቅም ሕዝብ ሆነው ይመለሳሉ።

9. እያለቀሱ ይመጣሉ፤እያጽናናሁ አመጣቸዋለሁ፤እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፣ኤፍሬም በኵር ልጄ ነውና፣በውሃ ምንጭ ዳር፣በማይሰናከሉበት ቀና መንገድ እመራቸዋለሁ።

10. “ሕዝቦች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ሩቅ ባሉ የባሕር ጠረፎችም፣‘እስራኤልን የበተነ እርሱ ይሰበስበዋል፤መንጋውንም እንደ እረኛ ይጠብቃል’ ብላችሁ ዐውጁ።

11. እግዚአብሔር ያዕቆብን ይዋጀዋልና፤ከእርሱም ከሚበረቱት እጅ ይታደገዋልና።

12. መጥተውም በጽዮን ተራራ ላይ በደስታ ይዘምራሉ፤ በእግዚአብሔርም ልግስና፣በእህሉ፣ በወይን ጭማቂውና በዘይቱ፣በፍየልና በበግ ጠቦት፣ በወይፈንና በጊደር ደስ ይሰኛሉ፤ውሃ እንደማይቋረጥባት የአትክልት ስፍራ ይሆናሉ፤ከእንግዲህም አያዝኑም።

13. ኰረዶች ይዘፍናሉ፤ ደስም ይላቸዋል፤ጐረምሶችና ሽማግሌዎችም ይፈነጥዛሉ፤ልቅሶአቸውን ወደ ደስታ እለውጣለሁ፤ከሐዘናቸውም አጽናናቸዋለሁ፤ ደስታንም እሰጣቸዋለሁ።

14. ካህናቱን አትረፍርፌ እባርካለሁ፤ሕዝቤም በልግስናዬ ይጠግባል፤”ይላል እግዚአብሔር።

15. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ዋይታና መራራ ልቅሶ፣ከራማ ተሰማ፤ልጆቿ የሉምና፣ራሔል አለቀሰች፤መጽናናትም እንቢ አለች።”

16. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ድምፅሽን ከልቅሶ፣ዐይኖችሽንም ከእንባ ከልክይ፤ድካምሽ ያለ ዋጋ አይቀርምና፤”ይላል እግዚአብሔር።“ከጠላት ምድር ይመለሳሉ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 31