ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 31:4-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. የእስራኤል ድንግል ሆይ፤ እንደ ገና አንጽሻለሁ፤አንቺም ትታነጪያለሽ፤ከበሮችሽንም እንደ ገና አንሥተሽ፣ከሚፈነጥዙት ጋር ትፈነድቂያለሽ።

5. እንደ ገናም በሰማርያ ኰረብቶች ላይ፣ወይን ትተክያለሽ፤አትክልተኞች ይተክሏቸዋል፤በፍሬውም ደስ ይላቸዋል።

6. ጠባቂዎች፣ በኤፍሬም ኰረብቶች ላይ፣‘ኑ፤ ወደ ጽዮን፣ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር እንውጣ!’ብለው የሚጮኹበት ቀን ይመጣል።

7. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ስለ ያዕቆብ በደስታ ዘምሩ፤ስለ ሕዝቦች አለቃ እልል በሉ፤ምስጋናችሁን አሰሙ፤‘እግዚአብሔር ሆይ፤ የእስራኤልን ቅሬታ፣ሕዝብህን አድን’ በሉ።

8. እነሆ፤ ከሰሜን ምድር አመጣቸዋለሁ፤ከምድርም ዳርቻ እሰበስባቸዋለሁ፤በመካከላቸውም ዕውሮችና አንካሶች፣ነፍሰ ጡርና በምጥ ላይ ያሉ ሴቶች ይገኛሉ፤ታላቅም ሕዝብ ሆነው ይመለሳሉ።

9. እያለቀሱ ይመጣሉ፤እያጽናናሁ አመጣቸዋለሁ፤እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፣ኤፍሬም በኵር ልጄ ነውና፣በውሃ ምንጭ ዳር፣በማይሰናከሉበት ቀና መንገድ እመራቸዋለሁ።

10. “ሕዝቦች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ሩቅ ባሉ የባሕር ጠረፎችም፣‘እስራኤልን የበተነ እርሱ ይሰበስበዋል፤መንጋውንም እንደ እረኛ ይጠብቃል’ ብላችሁ ዐውጁ።

11. እግዚአብሔር ያዕቆብን ይዋጀዋልና፤ከእርሱም ከሚበረቱት እጅ ይታደገዋልና።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 31