ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 31:29-35 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

29. “በዚያ ዘመን ሰዎች ዳግመኛ፣‘አባቶች በበሉት ጐምዛዛ የወይን ፍሬ፣የልጆች ጥርስ ጠረሰ’ የሚለውን ምሳሌ አይናገሩም።

30. ነገር ግን፣ እያንዳንዱ በገዛ ኀጢአቱ ይሞታል፤ ጐምዛዛ የወይን ፍሬ የሚበላ ሁሉ የራሱን ጥርስ ይጠርሳል።

31. “ከእስራኤል ቤትና፣ከይሁዳ ቤት ጋር” ይላል እግዚአብሔር፤“አዲስ ቃል ኪዳን የምገባበት፣ጊዜ ይመጣል።

32. ከግብፅ አወጣቸው ዘንድ፣እጃቸውን ይዤ በመራኋቸው ጊዜ፣ከአባቶቻቸው ጋር እንደ ገባሁት ኪዳንአይደለም፤የእነርሱ ባልገ ሆኜ ሳለሁ፣ቃል ኪዳኔን አፍርሰዋልና።”ይላል እግዚአብሔር።

33. “ነገር ግን ከዚያ ጊዜ በኋላ፣ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ኪዳን ይህ ነው” ይላል እግዚአብሔር፤“ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ፤በልባቸውም እጽፈዋለሁ።እኔ አምላክ እሆናቸዋለሁ፤እነርሱም ሕዝቤ ይሆናሉ።

34. ከእንግዲህ ማንም ሰው ባልንጀራውን፣ወይም ወንድሙን፣ ‘እግዚአብሔርን ዕወቅ’ ብሎ አያስተምርም፤ከትንሹ ጀምሮ እስከ ትልቁ፣ሁሉም እኔን ያውቁኛልና፤”ይላል እግዚአብሔር።“በደላቸውን ይቅር እላለሁ፤ኀጢአታቸውንም መልሼ አላስብም።”

35. በቀን እንድታበራ፣ፀሓይን የመደበ፣በሌሊት እንዲያበሩ፣ጨረቃንና ከዋክብትን ያዘዛቸው፣የሞገዱ ድምፅ እንዲተምም፣ባሕሩን የሚያናውጥ፣ስሙ የሰራዊት ጌታ የሆነ፣ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 31