ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 2:27-33 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

27. ዛፉን፣ ‘አንተ አባቴ ነህ’ድንጋዩንም፣ ‘አንተ ወለድኸኝ’ አሉ፤ፊታቸውን ሳይሆን፣ጀርባቸውን ሰጥተውኛልና፤በመከራቸው ጊዜ ግን፣‘መጥተህ አድነን’ ይላሉ።

28. ታዲያ፣ ልታመልካቸው ያበጀሃቸው አማልክት ወዴት ናቸው?በመከራህ ጊዜ ሊያድኑህ የሚችሉ ከሆነ፣ይሁዳ ሆይ፤ እስቲ ይምጡና ያድኑህ፤የከተሞችህን ቍጥር ያህል፣የአማልክትህም ብዛት እንዲሁ ነውና።

29. “ለምን በእኔ ታማርራላችሁ?ያመፃችሁብኝ እናንተ ሁላችሁ ናችሁ፤”ይላል እግዚአብሔር።

30. “ልጆቻችሁን በከንቱ ቀጣኋቸው፤እነርሱም አልታረሙም።ሰይፋችሁ እንደ ተራበ አንበሳ፣ነቢያታችሁን በልቶአል።

31. “የዚህ ትውልድ ሰዎች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል አስተውሉ፤“እኔ ለእስራኤል ሕዝብ ምድረ በዳ፣ወይስ ድቅድቅ ጨለማ ያለበት ምድር ሆንሁበትን?ሕዝቤ፣ እንደ ልባችን ልንሆን እንፈልጋለን፤ተመልሰንም ወደ አንተ አንመጣም’ ለምን ይላል?

32. ለመሆኑ ቆንጆ ጌጣጌጧን፣ሙሽራ የሰርግ ልብሷን ትረሳለችን?ሕዝቤ ግን፣እጅግ ብዙ ቀን ረስቶኛል።

33. በፍትወት ለማጥመድ እንዴት ስልጡን ነሽ?ልክስክስ ክፉ ሴቶች እንኳ ከመንገድሽ ብዙ ክፋት ይማራሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 2