ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 15:9-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. የሰባቶቹ እናት ትዝለፈለፋለች፤ትንፋሿም ይጠፋል፤ገና ቀን ሳለ ፀሓይዋ ትጠልቃለች፤እርሷም ታፍራለች፤ ትዋረዳለችም፤የተረፉትንም በጠላቶቻቸው ፊት፣ለሰይፍ እዳርጋቸዋለሁ፤”ይላል እግዚአብሔር።

10. ወይኔ እናቴ! ለምድር ሁሉ፣የጭቅጭቅና የክርክር ሰው የሆንሁትን ምነው ወለድሽ!ለማንም አላበደርሁም፤ ከማንም አልተበደርሁም፤ነገር ግን ሰው ሁሉ ይረግመኛል።

11. እግዚአብሔር እንዲህ አለ፤“በእርግጥ ለበጎ ዐላማ እታደግሃለሁ፤በመከራና በጭንቅ ጊዜም፣ጠላቶችህ ደጅ እንዲጠኑህ በእውነት አደርጋለሁ።

12. “ሰው ብረትን፣ ከሰሜን የመጣን ብረት፣ነሐስንስ መስበር ይችላልን?

13. በመላ አገርህ፣ስላለው ኀጢአትህ ሁሉ፣ሀብትና ንብረትህን፣ያለ ዋጋ አሳልፌ ለምርኮ እሰጣለሁ።

14. ቍጣዬ በላያችሁ፣የሚነድ እሳት ትጭራለችና፣በማታውቀው አገር፣ለጠላቶችህ ባሪያ አደርግሃለሁ።”

15. እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ታውቃለህ፤እንግዲህ አስበኝ፤ ጐብኘኝም፤አሳዳጆቼን ተበቀልልኝ።ታጋሽ እንደ መሆንህ አታጥፋኝ፤ባንተ ምክንያት የሚደርስብኝን ነቀፋ አስብ።

16. ቃልህ በተገኘ ጊዜ በላሁት፤የሠራዊት አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤በስምህ ተጠርቻለሁና፣ቃልህ ሐሤትና የልብ ደስታ ሆነልኝ።

17. ፈንጠዝያ ከሚያደርጉት ጋር አልተቀመጥሁም፤ከእነርሱም ጋር አልፈነጨሁም፤እጅህ በላዬ ስለ ነበር፣ በቍጣህ ስለ ሞላኸኝ፣ለብቻዬ ተቀመጥሁ።

18. ሕመሜ ለምን ጸናብኝ?ቍስሌስ ለምን በረታብኝ? ለምንስ የማይፈወስ ሆነ?እንደሚያታልል ወንዝ፣እንደሚያሳስት ምንጭ ትሆንብኛለህን?

19. ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ብትመለስ፣ መልሼ አቆምሃለሁ፤ታገለግለኛለህም፤የከበረውን ከማይረባው ለይተህ ብትናገር፣አፍ ትሆነኛለህ፤እነርሱ ወደ አንተ ይመለሳሉ እንጂ፣አንተ ወደ እነርሱ አትመለስም፤

20. ለዚህ ሕዝብ የናስ ቅጥር፣ የተመሸገየናስ ቅጥር አደርግሃለሁ፤ልታደግህና፣ ላድንህም፣እኔ ከአንተ ጋር ነኝና፤ቢዋጉህም እንኳ፣ሊያሸንፉህ አይችሉም፤”ይላል እግዚአብሔር፤

21. “ከክፉዎች እጅ እቤዥሃለሁ፤ከጨካኞችም ጭምደዳ እታደግሃለሁ።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 15