ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 40:9-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. እንደ እግዚአብሔር ክንድ ያለ ክንድ አለህን?ድምፅህስ እንደ እርሱ ድምፅ ሊያንጐደጒድ ይችላልን?

10. እንግዲያስ ክብርንና ልዕልናን ተጐናጸፍ፤ግርማ ሞገስንም ተላበስ፤

11. ቍጣህን አፍስስ፤ትዕቢተኛውን ሁሉ ተመልክተህ አዋርደው፤

12. ትዕቢተኛውን ሰው ሁሉ ተመልክተህ ዝቅ አድርገው፤ክፉዎችንም በቆሙበት ስፍራ አድቅቃቸው።

13. ሁሉንም በአንድ ላይ ከዐፈር ደባልቃቸው፤ፊታቸውንም በመቃብር ውስጥ ሸፍን።

14. እኔም ቀኝ እጅህ እንደምታድንህ፣በዚያን ጊዜ አረጋግጬ እቀበላለሁ።

15. “አንተን እንደ ፈጠርሁ፣ የፈጠርሁትን፣‘ብሄሞት’ ተመልከት፤እንደ በሬ ሣር ይበላል፤

16. ብርታቱ ወገቡ ውስጥ፣ኀይሉም በሆዱ ጡንቻ ላይ ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 40