ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 4:15-20 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

15. መንፈስ ሽው ብሎ በፊቴ አለፈ፤የገላዬም ጠጒር ቆመ።

16. እርሱም ቆመ፣ምን እንደሆነ ግን መለየት አልቻልሁም፤አንድ ቅርጽ በዐይኔ ፊት ነበረ፤በእርጭታ ውስጥ እንዲህ የሚል ድምፅ ሰማሁ፤

17. ‘ሥጋ ለባሽ ከእግዚአብሔር ይልቅ ጻድቅ ሊሆን ይችላልን?ሰውስ ከፈጣሪው ይልቅ ንጹሕ ሊሆን ይችላልን?

18. እግዚአብሔር በአገልጋዮቹ ላይ እምነት ካልጣለ፣መላእክቱንም በስሕተታቸው ከወቀሰ፤

19. ይልቁንስ በጭቃ ቤት የሚኖሩ፣መሠረታቸው ከዐፈር የሆነ፣ከብልም ይልቅ በቀላሉ የሚጨፈለቁ እንዴት ይሆኑ?

20. በንጋትና በምሽት መካከል ይደቃሉ፤ሳይታሰብም ለዘላለም ይጠፋሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 4