ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 39:1-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. “የበረሃ ፍየል የምትወልድበትን ጊዜ ታውቃለህን?ዋልያ ስታምጥስ ተከታትለህ አይተሃል?

2. የእርግዝናቸው ወራት ምን ያህል እንደሆነ ትቈጥራለህን?የሚወልዱበትንስ ጊዜ ታውቃለህን?

3. ተንበርክከው ይወልዳሉ፤ከምጣቸውም ጣር ይገላገላሉ።

4. ግልገሎቻቸውም ይጠነክራሉ፤ በሜዳም ያድጋሉ፤ተለይተው ይሄዳሉ፤ ወደ እነርሱም አይመለሱም።

5. “ለሜዳ አህያ ነጻነት የሰጠው ማን ነው?እስራቱንስ ማን ፈታለት?

6. ምድረ በዳውን መኖሪያው፣የጨውንም ምድር ማደሪያው አድርጌ ሰጠሁት።

7. በከተማ ውካታ ይሥቃል፤የነጂውንም ጩኸት አይሰማም።

8. በየተራራው ይሰማራል፤ሐመልማሉንም ሁሉ ለማግኘት ይወጣል።

9. “ጐሽ ያገለግልህ ዘንድ ይታዘዛልን?በበረትህስ አጠገብ ያድራልን?

10. እንዲያርስልህ ልትጠምደው ትችላለህ?ወይስ እየተከተለህ ዕርሻህን ይጐለጒልልሃልን?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 39