ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 38:10-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. ድንበር ወሰንሁለት፤መዝጊያና መወርወሪያውን አበጀሁለት።

11. ‘እስከዚህ ድረስ ትመጣለህ፤ ማለፍ ግን አትችልም፤የዕቡይ ማዕበልህም ገደብ ይህ ነው’ አልሁት።

12. “ከተወለድህ ጀምሮ ንጋትን አዘህ ታውቃለህን?ወይስ ወጋገን ስፍራውን እንዲይዝ አድርገሃል?

13. በዚህም የምድርን ዳርቻ ይዞ፣ክፉዎችን ከላይዋ እንዲያራግፍ አድርገሃልን?

14. ምድር ከማኅተም በታች እንዳለ የሸክላ ጭቃ ቅርጿ ይወጣል፤ቅርጿ እንደ ልብስ ቅርጽ ጐልቶ ይታያል።

15. ክፉዎች ብርሃናቸውን ተከልክለዋል፤ከፍ ያለው ክንዳቸውም ተሰብሮአል።

16. “ወደ ባሕር ምንጭ ወርደህ ታውቃለህን?ወይስ ወደ ጥልቀቱ ገብተህ በመሠረቱ ላይ ተመላልሰሃልን?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 38