ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 33:5-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. የምትችል ከሆነ መልስልኝ፤ተዘጋጅተህም በፊቴ ቁም።

6. በእግዚአብሔር ፊት እኔም እንዳንተው ነኝ፤የተፈጠርሁትም ደግሞ ከዐፈር ነው።

7. እኔን መፍራት የለብህም፤እጄም ሊከብድብህ አይገባም።

8. “በእርግጥ የተናገርኸውን ሰምቻለሁ፤እንዲህም ስትል አድምጫለሁ፤

9. ‘ኀጢአት የሌለብኝ ንጹሕ ነኝ፤ከበደል ነጻ ነኝ፤ እድፈትም የለብኝም፤

10. እግዚአብሔር ግን ሰበብ ፈልጎብኛል፤እንደ ጠላቱም ቈጥሮኛል፤

11. እግሬን በግንድ አጣብቆአል፤እንቅስቃሴዬንም ሁሉ ይከታተላል።’

12. “ነገር ግን እግዚአብሔር ከሰው ስለሚበልጥ፣ትክክል እንዳልሆንህ እነግርሃለሁ።

13. የሰውን አቤቱታ እንደማይሰማ፣ለምን ታማርርበታለህ?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዮብ 33